Psalms 121

የእስራኤል ጠባቂ

መዝሙረ መዓርግ።

1ዐይኖቼን ወደ ተራሮች አነሣሁ፤
ረድኤቴ ከወዴት ይመጣል?
2ረድኤቴ ሰማይንና ምድርን ከፈጠረ፣
ከእግዚአብሔር ዘንድ ይመጣል።

3እግርህ እንዲሸራተት አይፈቅድም፤
የሚጠብቅህም አይተኛም።
4እነሆ፤ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም፤ አያንቀላፋምም።

5 እግዚአብሔር ይጠብቅሃል፤
እግዚአብሔር በቀኝህ በኩል ይከልልሃል።
6ፀሓይ በቀን አያቃጥልህም፤
ጨረቃም በሌሊት ጕዳት አታመጣብህም።

7 እግዚአብሔር ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሃል፤
ነፍስህንም ይንከባከባታል።
8 እግዚአብሔር ከአሁን ጀምሮ እስከ ዘላለም፣
መውጣትህንና መግባትህን ይጠብቃል።
Copyright information for AmhNASV